RIDE ከእናት ባንክ ጋር በመተባበር ለቅንጡና ዘመናዊ መኪኖች የፋይናንስ ብድር ሰጠ

Enat Bank and RIDE collaborated to give loans to RIDE Drivers.

RIDE ከእናት ባንክ ጋር በመተባበር ቅንጡና ዘመናዊ መኪኖች የፋይናንስ ብድር ያመቻቸ ሲሆን በዛሬው እለት መኪኖቹን አስመርቆ ወደስራ አስገብቷል::

ከዚህ ቀደም እናት ባንክ ለራይድ አሽከርካሪዎች ባዘጋጀው ብድር መሰረት በሺዎች የሚቆጠሩ አባላት ግብራቸውን በወቅቱ ለመክፈል ፣ አደጋ ሲገጥማቸው ጥገና ለማከናወን እንዲሁም ማንኛውም ማህበራዊ ችግር ሲገጥማቸው እክላቸውን በፍጥነት ለመፍታት እንደ እናት አለኝታነቱን ያሳየ ሲሆን ፣ አሁን ደግሞ ትጉህ የራይድ ቤተሰብ አባላት የ2022 ሞዴል ዘመናዊ መኪና ባለቤት እንዲሆኑ በተግባር እየሰራ ይገኛል::
ዛሬ ነሃሴ 19/2014 ዓም ዝግጅት ላይ የእናት ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሚያስ አንዳርጌ እንደተናገሩት ባንካቸው በቀጣይነት ይህንን እድል አስፍቶ ተግተው የሚሰሩ የራይድ አሽከርካሪዎችን ለማዳረስ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው ፣ እንደቤት የመሳሰሉ የብድር አይነቶችንም ለማካተት እቅድ መያዙን ጠቅሰዋል:: የራይድ ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሳምራዊት ፍቅሩ ለራይድ ቤተሰብ አባላት ባስተላለፉት መልዕክት በቀጣይ የአጭር ግዜ አነስተኛ መጠን ብድርም ሆነ የረጅም ግዜ ትልቅ መጠን የብድር አገልግሎት ላይ ለመሳተፍ በእናት ባንክ ፈጥነው አካውንት ከፍተው ቁጠባ እንዲጀምሩ አስገንዝበዋል:: በዝግጅቱም በዛሬው የብድር አገልግሎት መኪና ያገኙ አባላት ደስታቸውን የገለፁ ሲሆን ሌሎች አባላትም ከራይድና ከእናት ባንክ ጋር እየሰሩ የሚመጡ እድሎችን እንዲጠቀሙ በአፅኖት አሳስበዋል።

Share:

More Posts

Send Us A Message

Scroll to Top